Sunday, November 17, 2013

ኧረ ጎበዝ ምን ነካን?!

እኔ የምለው፣ ትችትን ወይም ተቃውሞን ያለስድብ መግለጽ አይቻልም እንዴ? በፌስቡክ ላይ በተለያዩ ዘርፎች ላይ ከሚሰጡ አስተያየቶች መካከል ብዙዎቹ ስድብና ዘለፋን ያዘሉ መሆናቸው በግሌ በጣም ያሳስበኛል፡፡ ያልተስማማንበትን ነገር ሲሆን በምክንያት፣ ካልሆነም እንዲሁ ”አልተስማማሁበትም” ብሎ መቃወም ሲቻል፣ በተራ የመንደር ስድቦች እና ጸያፍ ቃላት መዝለፍ ”ምን እየሆንን ነው? ”የሚያሰኝ ነው፡፡ ይህንን ለመረዳት በፌስቡክ ላይ ከወጡ በርካታ ዜናዎች ሥር የሚጻፉ አስተያየቶችን ማየት ይቻላል፡፡ እኔ ግን በተለይ ትኩረቴን የሳበውን አንድ ጉዳይ ብቻ አንስቼ የታየኝን ልል ወደድኩ፡፡
ከጥቂት ሳምንታት በፊት ቴዲ አፍሮ ”መሬት ሲመታ” በሚል ርዕስ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማበረታቻ አንድ ነጠላ ዜማ ለቀቀ፡፡ ይህም በፌስቡክ ላይ ተገለጸ፡፡ እንደተለመደውም ብዙ አስተያየቶች ተሰጡ፡፡ ከአስተያየቶቹ ውስጥ በርከት ያሉ አሉታዊ ትችቶች ባልተለመደ ሁኔታ ነበሩበት፡፡ ትችቱ ባልከፋ ፣ ግን፣ሁሉም ትችቶች በተራ ስድብ እና ዘለፋ የተሞሉ፣ ምክንያታዊ ያልሆኑ መሆናቸው ነው ችግሩ፡፡ ቴዲ ዋሊያዎችን ለማበረታታት፣ እኛን ደጋፊዎቻቸውንም ለማጠንከር በሙያው አንድ አስተዋጽኦ ሲያደርግ፣ ማመስገኑ እና ማድነቁ ቢቀር  እንዴት ሰብዕናን በሚያዋርድ መልኩ፣ያውም ሥራውን ሳናደምጥ፣ ለዘለፋ እንቸኩላለን? አያይ! በጣም ችግር አለብን፡፡
አንዳንዶች ”ቴዲ ዘገየ ” ይላሉ፤ ሌሎች ደግሞ ”ቴዲ ራስ ወዳድ፣ ገንዘብ አፍቃሪ፣ ሳንቲም ለቃሚ፣ እና ስግብግብ ነው” ሲሉ ይሰማል (ይነበባል)፡፡ ሁሉም አሉታዊ ትችቶች መሠረት የሌላቸው እና ”ውሃ የማያነሱ” ናቸው ባይ ነኝ፡፡ ከሙያዊ ማንነቱም ሆነ ከግላዊ ሰብዕናው ጋር የማይገናኙ እና፣ ምናልባትም፣ የቅናት የሚመስሉ፡፡ ከላይ ያነሳሁዋቸውን ”አስተያየቶች” እስቲ ተራ በተራ እንመልከት፡፡
1.      ቴዲ ዘግይቷል፡ ይህንን አስተያየት የሚሰጡ ሰዎች መነሻቸው (በእኔ ግምት) ”ብሔራዊ ቡድናችን በኢንተርናሽናል መድረኮች ረዥም ርቀት ከተጓዘ እና ቡድኑን የሚያሞግሱ በርካታ ሙዚቃዎች ከወጡ በኋላ የቴዲ ”መሬት ሲመታ” መምጣቱ ስህተት ነው” የሚል ነው፡፡ እኔ እንደማምነው ግን የጥበብ ሥራ ሰፊ ጊዜን፣ ትኩረትን፣ እና ጥሞናን ይፈልጋል፡፡ ቴዲም ያለውን ሁኔታ በጥሞና ከተመለከተ በኋላ ‘ለሁላችንም ያስፈልገናል’ ብሎ ያመነበትን ሐሳብ ተገቢ ነው ባለው ጊዜ በሙዚቃ አቀረበልን፡፡ ይህ መዘግየት አይመስለኝም፡፡ ወቅታዊነትን መጠበቅ፣ ያላየነውን ጎን ማሳየት፣ እና ማበረታታት እንጂ፡፡
2.     ቴዲ ራስ ወዳድ ነው፡ ”ራስ ወዳድነት” ምንድን ነው? ራስ ወዳድነት ከራስ አልፎ ማየት አለመቻል፣ ”እኔን ከተመቸኝ ሌላው ምናባቱ” ማለት፣ ወዘተ ይመስለኛል፡፡ የቴዲ ታሪክ ይህ አለመሆኑን ሁላችንም እናውቀዋለን፡፡ ቴዲ በሙያው ያገኘውን ዕውቅና ለመልካም ሲያውለው በተደጋጋሚ አይተናል፡፡ የቅርቡን እንኳን ብንወስድ፣ ከእስር ከተፈታ በኋላ ካቀረበው የመጀመሪያ ኮንሰርት አንዲት ሳንቲም ለራሱ ሳይወስድ ለበጎ አድራጎት ድርጅት መስጠቱ፣ ከራሱ ኪስም አውጥቶ ሌላ የበጎ አድራጎት ድርጅትን መርዳቱ፣ በእጁ በቂ ገንዘብ ሳይኖረው እንኳ ራሱን ባለዕዳ አድርጎ በሶማሌላንድ የሞት ፍርድ የተፈረደበትን ወገናችንን የደም ዋጋ ከፍሎ ከሰይፍ ማስጣሉ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ታዲያ የት ላይ ነው የቴዲ ራስ ወዳድነት?
3.     ቴዲ ገንዘብ አፍቃሪ ነው፡ የዚህኛው ትችት መነሻ ደግሞ ”ቴዲ የሙዚቃ ዝግጅቶችን የሚያቀርበው ገበያውን እና የሚከፈለውን ገንዘብ እያየ ነው” የሚል ይመስለኛል፡፡ እንዴ?! ሁላችንስ ብንሆን በየሥራ ዘርፋችን የተሻለ ክፍያ የምናገኝበትን አይደል እንዴ የምንመርጠው? ታዲያ ይህ የሁላችንም ፍላጎት ቴዲ ጋር ሲደርስ ሀጢያት የሚሆነው ለምንድን ነው? የተሻለ ክፍያ የምንጠይቀው እኮ የሚከፈለን ክፍያ ሥራችንን የሚመጥን መሆን ስላለበት ነው፡፡ ቴዲም እኛ ዛሬ እንድናደንቀው እና መነጋገሪያ እንዲሆነን ያስቻሉትን ሥራዎቹን በሚመጥን ክፍያ ማቅረቡ የሰው ፍላጎት፣ የንግድ አሠራር መንገድም ነው እንጂ ወንጀል አይደለም፡፡
4.     ቴዲ  ሳንቲም ለቃሚ ነው፡ አንድ ሰው በሚሠራው ሥራ ፈላጊ ያለበትን ቦታና ጊዜ መምረጥ አለበት፡፡ የዚህኛው ትችት አቅራቢዎች እንደ ማጠናከሪያ የሚያቀርቡት አምና በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው እና አገራችን ከ31 ዓመታት በኋላ በተሳተፈችበት የአፍሪካ ዋንጫ ዋዜማ በጆሐንስበርግ ኮንሰርት ማቅረቡን ነው፡፡ ካዋጣው ለምን አያደርገውም? ሥራው እስከሆነ ድረስ እና ወቅቱም አመቺ ሆኖ ከተገኘ በዚያ የሚገኙ ወገኖቹን አዝናንቶ ለሥራው ቢከፈለው ነውሩ ምንድን ነው? ”ሳንቲም መልቀም” እኮ ለ”ሳንቲሟ” ሲባል ”ከፍራሹም፣ ከጭቃውም ላይ መውደቅ”  ነው፡፡ ቴዲ ደግሞ ይህንን ሲያደርግ እስካሁን አላየንም፡፡
5.     ቴዲ ስግብግብ ነው፡ ይህኛው ምንም ማብራሪያ የማያስፈልገው ”ባዶ እና ተራ ዘለፋ” ነው እላለሁ፡፡ ሥራን ሠርቶ ገንዘብ  ማግኘት፣ ካገኙት ገንዘብ ላይ ለመልካም ተግባር መስጠት ”ስግብግብነት” ነው  የሚል ካለ፣ አዕምሮውን መመርመር አለበት፡፡ የቴዲን ”ስግብግብነት” በማስረጃ ያቀረበ አንድም የፌስቡክ ተቺ የለም፡፡ ለዚህ ነው ”ባዶ እና ተራ ዘለፋ” ነው ያልኩት፡፡ ማስረጃ ያስፈልጋል፡፡
በአጠቃላይ የቴዲንም ሆነ የማንኛውንም የሙዚቃ ባለሙያ ሥራ ሳናዳምጥ እና መልዕክቱን ሳንረዳ፣ ጫፍ ይዘን መሮጥ አላዋቂነት ነው ባይ ነኝ፡፡ በተጨማሪም የአንድን ሰው ግላዊ ማንነት ከሙያዊ ማንነቱ ጋር አደባልቆ ማየትም ፍርደ-ገምድልነትን ያመጣል እላለሁ፡፡ አንድ ምሳሌ እንይ፡፡ ጥላሁን ገሠሠን የአገራችን የሙዚቃ ንጉሥ አድርገን የሾምነው፣ ከትውልድ እስከ ትውልድ፣ ከትናንት እስከ ዛሬ ያደነቅነው፣ የወደድነው፣ እና ያከበርነው፣ በሞቱም ጊዜ አደባባይ ወጥተን፣ በጸሐይ እየተጠበስን በታላቅ ለቅሶ የሸኘነው እና በብሔራዊ ጀግና ክብር የቀበርነው በሥራዎቹ ጥራት እና ታላቅነት ነው እንጂ የግልና የቤተሰብ ሕይወቱማ ለአርአያነት እንደማይበቃ ጠፍቶን አይደለም፡፡ ቴዲም እንደግለሰብ ድክመቶች ሊኖሩበት እንደሚችል ሳንረሳ ያንን ለራሱ ትተን ሥራዎቹን በማስተዋል ብንመዝን ከስህተት እንድናለን፡፡
ቴዲን አለመውደድ መብት ነው፣ ሥራውን አለማድነቅም እንዲሁ፡፡ ነገር ግን ስንተች ስድብ እና ዘለፋን አስወግደን ለመማማርና ለመተራረም ልናውለው ይገባል፡፡ ”በፌስቡክ ላይ የሚሰጡ በቁጥር ቀላል የማይባሉ አስተያየቶች በስድብ መታጀባቸው ኢትዮጵያዊ ጨዋነታችን የት ገባ?” የሚያሰኝ ነው፡፡ ኧረ ጎበዝ ምን ነካን?

Monday, July 29, 2013

Fixing the Blurry Glasses

The afternoon of Friday, July 12, saw a somewhat "bizzare" incident at London's Heathrow Airport. A smoke was seen on the tail of an Ethiopian Airlines Boeing 787 Dreamliner. The international media made the incident their headline story since late Friday (at least for 24 hours). The amazing thing was, the smoke (probably caused by a fire ignited by "transmission problem", as concluded by investigators) was triggered eight hours after the aircraft was parked at the airport.
I think the Heathrow incident made the headlines not for the fact that the plane is an Ethiopian property. Rather, it was for two other reasons; One: the incident happened on British soil, and two: it happened on a plane that is "equipped with the latest technology." For whatever reason, the incident turned people's heads to our country one more time.
What moved me to write this post wasn't the Heathrow incident. It is rather the comments and responses that came after the news broke out. A considerable number of people, mainly from the western world, were amazed by the fact that Ethiopia actually owns a Dreamliner, even has an airliner. Some even went further to express their disbelief that Ethiopians manage to "eat at all," let alone having their own flag carrier. 
It makes me sick to hear and see people from the so-called "First World" to disregard the "Third World" in an uncivilized way. They sometimes claim to know the nature, behavior, and fate of the people of Africa, Latin America, and Asia as the palm of their hands. In the case of Ethiopia, they think the entire nation became a bare-land after the 1984/85 drought, they were the only ones who saved the day.  They consider a skinny person an Ethiopian, and the people from Ethiopia are "good-for-nothing." They tend to believe we're doomed to live and die poor and starved. Hypocrites!
I believe it's time to tell the facts to those who do not know (or blindfold themselves not to know) the truth. Their racist and fictionally-driven "superior mentality" must be eradicated once and for all. It's time to fix the blurry eyeglasses of "the white folks!"

A lesson in History
Aircraft began to flew over Ethiopian skies long before the establishment of the Ethiopian Airlines. A French pilot, Andrẻ Maillet, flew a twin-engined Potez aircraft from Djibouti, and landed at Jan Meda in Addis Ababa on August 18, 1929. With the threat of the Fascist Italian invasion plans, according to the renowned historian, Prof. Richard Pankrust, the Ethiopian government of the day has ordered two more aircraft from Germany, even though  the delivery was delayed by the French authorities at Djibouti in order to make the French aircraft arrive first. 
After the return of the government after the Italian invasion of 1935-41, Emperor Haileselassie took up the concept of establishing a national airliner seriously, and asked the governments of the US, the UK, and France to help in this endeavor. His efforts have finally paid off, and on 8 September, 1945, the American airliner, TWA, signed an agreement with John Spencer, who was the foreign affairs advisor to the emperor, to establish a commercial airline for Ethiopia.(Historical Dictionary of Ethiopia, 2004).
Over the coming years, the airline has made tremendous developments in its activities; such as expanding its routes, replacing personnel from TWA (one such a notable appearance was the introduction of the first African jet pilot, Capt. Alemayehu Abebe), and the acquisition of some of the modern aircraft to date, including the landmark products of Boeing like the B767 (1984) and B787 Dreamliner (2012).
The success of the Ethiopian Airlines over the last 67 years have placed Ethiopia on the world map, as one of Africa's modern nations. Unlike some 'ferenjis,' who are ignorant of such developments, this airline has exhibited strength, dedication, and commitment as the springboards of its success. It is a success that hasn't been interrupted by the succession of governments, famine, wars, or any other mishaps in the country over the years.   
I was pretty much amazed and inspired by the long success story of Ethiopian Airlines for so long, especially by the time I was doing a research on the passenger transport services of the airline about 11 years ago when I was a student at the Addis Ababa University. The success, came with tireless efforts by the staff and management of the company, and even with sacrifices made by the loss of lives, are exemplary for all of the "Third World" nations in showing the way to success without the so-called "Superpowers" breathing at their necks. And Ethiopians are always proud of their national carrier.
Africa's First Dreamliner, "Queen of Sheba". Photo: from Wikipedia
There has been a lot to tell those who doubt Ethiopia can achive so much in the airline industry. But I think it is better to leave that to themselves to find out, since a lot can be found from the archives, and the internet. Their comments, which might come just out of jealousy of the fact that we have the Dreamliner before the Europeans and the Americans, or just of ignorance, are baseless. And so they need to learn history, and redeem themselves for their racist views.
So there you have it, you doubters! Believe it or not: We have an airline, and we have the Dreamliner (five of them, actually). We have pilots, flight attendants, and technicians that bring our national colors to the sky. We have the facilities to train airline personnel from all around the world, maintain aircraft from any part of the globe, and we have more than half-a-century's experience in flying under our belt. Stop being narrow minded, and start digging for history. We're not only of famine and poverty. We have so many success stories to tell, and we're a proud nation. And there's nothing you can do about it!
Long Live Ethiopia!